BBC News, አማርኛ - ዜና
ዜና
ቀጥታ, አሜሪካ በሳምንታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ኢራን ላይ ጥቃት ስትፈጽም፤ ቴህራን የአጸፋ እርምጃ ወሰደች
የአሜሪካ ጦር ከሐምሌ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በኢራን በፈጸመው ጥቃት ላራክ ደሴት ላይ የሚገኙ ማስወንጨፊያዎችን መምታቱን አንድ የዋሽንግተን ባለሥልጣን ተናገሩ። የኢራን አብዮታዊ ዘቡ በበኩሉ፣ በዮርዳኖስ የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ዒላማዎች ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።
በቀይ ባሕር እንቅስቃሴ ላይ ስጋት የፈጠረው እና ሚሊዮኖች የሚጠየቅበት የሶማሊያ ባሕር ላይ ውንብድና
ባለፈው ሳምንት በአራት ቀናት ውስጥ ሁለት የንግድ ጭነት መርከቦች በኤደን ባሕረ ሰላጤ በባሕር ላይ ዘራፊዎች ተይዘዋል። ይህም ከዓመቱ መጀመሪያ አንስቶ የተጠለፉ መርከቦች ቁጥርን ቢያንስ 13 እንዲደርስ አድርጓል። ይህ ክስተት የባሕር ላይ ወንበዴዎችን ለመከላከል እስካሁን ታይቶ የማያውቅ የድሮን ጥቃት እንዲካሄድ ምክንያት ሆኗል።
ቢቢሲ አማርኛ በቲክቶክ
አስተማማኝ ዜና እና መረጃን ቅድሚያ ለማግኘት ቢቢሲ አማርኛን ቲክቶክ ላይ ይከተሉ
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቪድዮዎች
ቪዲዮ, ግብፅ ትቀላቀለዋለች እየተባለ ያለው ቱርክ፣ ሳዑዲ እና ፓኪስታን የመሠረቱት 'የሙስሊም ኔቶ'
ቱርክ፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ፓኪስታን 'የመካ ስምምነት'ን ከፈረሙ ከአንድ ሳምንት በላይ ሆኗቸዋል። አንዳንድ ተንታኞች አገራቱ የተፈራረሙትን የመከላከያ ስምምነት "የሱኒ ስምምነት" ወይም "የሙስሊም ኔቶ" ሲሉ ጠርተውታል። አንዳንዶች እንደ ኢራን እና እስራኤል ላሉ አገራት የተላለፈ መልዕክት አድርገው አቅርበውታል። ሌሎች ደግሞ ይህ ስምምነት አገራቱ ለደኅንነት ዋስትና በዩናይትድ ስቴትስ ላይ ያላቸውን ጥገኝነት ለመቀነስ ያላቸውን ፍላጎት የሚያንፀባርቅ ነው ይላሉ። ነገር ግን ሙሉው ስምምነት ለሕዝብ ይፋ ባለመሆኑ እየተሰሙ ያሉት መላምቶች ብቻ ናቸው።
ቪዲዮ, “ጦርነት ከተጀመረ መንግሥታት ይለወጣሉ፤ ድንበሮች ይቀየራሉ”
ቢቢሲ በኢትዮጵያ እና በቀጣናዊ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ባጫ ደበሌ ጋር ቃለ መጠይቅ አድርጓል። የኢትዮጵያ አሁናዊ ሁኔታ፣ ከህወሓት ጋር ያለው ውዝግብ፣ የባሕር በር ጥያቄ እና የቀጠናዊ የጦርነት ስጋቶች በቃለ መጠይቁ ተዳሰዋል። በተለይም በአፍሪካ ቀንድ ቀጣናዊ ጦርነት ከተጀመረ ውጤቱ መሠረታዊ ለውጥን የሚያስከትል ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
ቪዲዮ, ኢትዮጵያዊው የማይክሮሶፍት ባለሙያ ስለኤአይ ጥቅም እና ጉዳት ምን ይላሉ?
ዓለማችንን በማይታመን ፍጥነት እየለወጠ ያለውን ሰው ሠራሽ አስተውሎት (ኤአይ) በአግባቡ መገንዘብ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ እየሆነ የመጣ ይመስላል። ስለ ሰው ሠራሽ አስተውሎት የተዛቡ ምልከታዎች ምንድን ናቸው? ለወደፊቱ የኤአይ ዓለም እንዴት እራሳችንን ማዘጋጀት እንችላለን? የሚሉና ተያያዥ ጥያቄዎችን በተመለከተ ኢትዮጵያዊው የማይክሮሶፍት ባለሙያ ዶ/ር ግርማው አበበ ታደሰ ምላሽ ሰጥቷል።
የቢቢሲ አማርኛ ዩቲዩብ ቻናልን ይቀላቀሉ
አነጋጋሪ ጉዳይ
በሳዑዲ ነሐሴ ላይ ብቻ ቢያንስ 60 ኢትዮጵያውያን ከዕፅ ጋር በተያያዙ ጥፋቶች መያዛቸውን ዘገባዎች አመለከቱ
ከዕፅ ጋር በተያያዙ ጥፋቶች የሚፈረደቸባው ሰዎችን በሞት እየቀጣች ባለችው ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ፣ በነሐሴ ወር ብቻ ጫትን ጨምሮ የተለያዩ ዕፆችን በማጓጓዝ የተጠረጠሩ ቢያንስ 60 ኢትዮጵያውያን በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ዘገባዎች አመለከቱ። ትናንት ረቡዕ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም. ተጨማሪ 15 ኢትዮጵያውያን ከ290 ኪሎ ግራም ጫት ጋር መያዛቸው ተዘግቧል።
ኢዜማ ከአገራዊ ምክክሩ ጋር በተያያዘ አምስት ማሳሰቢያዎች ሰጠ
በአገራዊ ምክክሩ ላይ ከተሳተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ የሆነው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ (ኢዜማ)፣ በቀጣይ የምክክር ሂደቱ ምዕራፎች መተግበር አለባቸው ያላቸውን አምስት ማሳሰቢያዎች ይፋ አደረገ። ኢዜማ፣ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ ተመካካሪዎች በሙሉ ድጋፍ ያልፈረሙባቸውን ምክረ-ሐሳቦች እንደማይቀበል ጨምሮ አስታውቋል። 4000 ተመካካሪዎችን አሳትፎ ከሐምሌ 8 ጀምሮ ከአንድ ወር በላይ የተካሔደው እና በርካታ ጥያቄዎች የተነሱበት የምክክር ሂደት ቅዳሜ ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም. በተካሔደ የመዝጊያ ሥነ ሥርዓት ተጠናቅቋል።
በርካታ ምዕራባውያን አገራት "በአፍሪካ ኅብረት ለሚመራው የሰሜን ኢትዮጵያ የማሸማገል ጥረት" ድጋፋቸውን ገለጹ
የአፍሪካ ኅብረት ፌደራል መንግሥት እና የህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮችን ለማሸማገል የሚያደርገውን ጥረት እንደሚደግፉ የአውሮፓ ኅብረት አባል የሆኑ የ22 አገራት እንዲሁም የዩናይትድ ኪንግደም፣ ኖርዌይ እና ካናዳ ኤምባሲዎች አስታወቁ። አገራቱ፣ "ክፉኛ በድርቅ በተጎዳው" ትግራይ ክልል የሚጀመር ወታደራዊ ግጭት ለሰሜን ኢትዮጵያ ሕዝብ "አስከፊ" እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል።
የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች የተገደሉበት ጥቃት እንዲመረመር በደቡብ ሱዳን የሚገኘው ኤምባሲ ጠየቀ
በጁባ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት ሁለት የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ወታደሮች ስለተገደሉበት ጥቃት ምርመራ እንዲደረጉ ጠየቀ። የተባበሩት መንግሥታት የደቡብ ሱዳን ተልዕኮ ባወጣው መግለጫ፣ በተፈጸመው "ደፈጣ ጥቃት" ሰላም ማስከበር ላይ የተሰማሩ ሁለት ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ሲገደሉ ሰባት ሰዎች እንደቆሰሉ አስታውቋል።
የፕሪቶሪያ አደራዳሪው ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ በትግራይ ክልል "ድንገተኛ ጉብኝት" ማድረጋቸው ተገለጸ
ከፕሪቶሪያ ስምምነት አደራዳሪዎች አንዱ የሆኑት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ ትናንት ሰኞ በትግራይ "በድንገተኛ ጉብኝት" ማድረጋቸውን ህወሓት የሚመራው የክልሉ አስተዳደር አስታወቀ። ህወሓት መሩ አስተዳደር ከፌደራል መንግሥት ጋር ውይይት ለመጀመር "መሠረታዊ እና ቁልፍ" ናቸው ያላቸውን ቅድመ ሁኔታዎች አስቀምጧል።
ግብፅ "በኃይል የባሕር በር ለማግኘት ከሚደረግ ሙከራ መቆጠብ" እንደሚገባ ገለጸች
የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ፣ "ከዓለም አቀፍ ሕግ ውጭ በኃይል የባሕር በር ለማግኘት" የሚደረጉ ጥረቶች መቆም እንዳለባቸው ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት የአረብ እና የአፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ተናገሩ። የግብፁ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በአፍሪካ ቀንድ "የሚገኙ አገራት "አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት" መጠበቅ እንዳለበት ገልጸዋል።
በአዲስ አበባ ጉዳይ ላይ የክልል ፕሬዝደንቶች ሰጡ የተባለው አስተያየት እና የጎላው ልዩነት
ወደ ማጠናቀቂያው በተቃረበው የአገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የአዲስ አበባ ጉዳይ መግባባት ያልተደረሰበት እና ሂደቱን ያዘገየ አጀንዳ ሆኗል። ሐሙስ ዕለት በተካሄደው ጉባኤ ላይ አዲስ አበባን በተመለከተ ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ስለተነሱት ምክረ ሀሳቦች ምንጮች ለቢቢሲ ተናግረዋል። የኦሮሚያ እና አማራ ክልሎች አመራሮች መካከል በመዲናዋ ጉዳይ ልዩነት መታየቱንም ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል።
ቢቢሲ አማርኛን በዋትስአፕ ላይ ያግኙ
የመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት
ግብፅ ትቀላቀለዋለች እየተባለ ያለው ቱርክ፣ ሳዑዲ እና ፓኪስታን የመሠረቱት 'የሙስሊም ኔቶ'
ቱርክ፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ፓኪስታን 'የመካ ስምምነት'ን ከፈረሙ ከአንድ ሳምንት በላይ ሆኗቸዋል። አንዳንድ ተንታኞች አገራቱ የተፈራረሙትን የመከላከያ ስምምነት "የሱኒ ስምምነት" ወይም "የሙስሊም ኔቶ" ሲሉ ጠርተውታል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን ቀጣናዊ ፖሊሲ የለወጠው የኢራን ጦርነት
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከአሜሪካ እና ከእስራኤል ጋር ባላት ግንኙነት የተነሳ የኢራን ዋነኛ ዒላማ ከሆነች በኋላ በቀጣናው አገራት ላይ ያላት መተማመን እየቀነሰች ነው። ለፖለቲካ፣ ለምጣኔ ሃብት እና ሌሎች ፍላጎቷን ለማሟላት ከቀጣናው ውጭ መመልከትን መርጣለች። ለዚህም ከሕንድ፣ ከዩክሬን፣ ከግሪክ፣ ከቆጵሮስ እና ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ትስስር እያጠናከረች ነው።
የኢንተርኔት ዳታን በመቆጠብ የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽን በቀላሉ ማንበብ ይፈልጋሉ?
የቢቢሲ አማርኛን ድረ ገጽ በቀላሉ በመክፈት ዜና እና ታሪኮችን በጽሑፍ ብቻ ያንብቡ!
ከየፈርጁ
እስከ ግማሽ ሚሊዮን ብር የሚወጣባቸው ግዙፍ የሽምግልና አበባዎች፡ የአበባ አብዮት ወይስ የባህል ለውጥ?
ከጋብቻ በፊት የሚደረገው የሽምግልና ሥነ ሥርዓት ከፍተኛ ድግስ እና ገንዘብ የሚፈስበት እየሆነ መጥቷል። ከሚዘጋጀው ድል ያለ ድግስ ባሻገር በመቶ ሺዎች ብር የሚያስወጡ ቄንጠኛ ግዙፍ የአበባ ‘እቅፎች’ ደግሞ የሽምግልናው ሥርዓት አካል ሆነዋል። በተለይ የሚቀርበው የአበባ ስጦታ መነጋገሪያ ሆኗል። የሽምግልና ሥነ ሥርዓት የሰርግን ቦታ እየተካ ነው? ግዙፉ የአበባ ስጦታስ ከየት የመጣ ልማድ ነው?
ባለ ፓስፖርት አይጦች እና ስለ ቲቢ የሚመራመሩት ኢትዮጵያዊ
አይጦች በጎ ስም የላቸውም፤ ሰዎች ከቤታቸው፣ ምግብ እና የተለያዩ እቃዎች ከሚያስቀምጡባቸው ሥፍራዎች አይጦችን ለማራቅ መርዝ ወይም መጥመድ ይጠቀማሉ። በአጠቃላይ አይጦች ከጥፋት ጋር ስለሚያያዙ በበርካቶች ዘንድ የተጠሉ ናቸው። ኢትዮጵያዊው ሳይንቲስት ምርምር የሚያደርጉባቸው ባለ ፓስፖርት አይጦች ግን ለሰው ልጅ ጤና እና ደኅንነት ከፍተኛ ጥቅም አላቸው።
"አዳም አንድ ደራሲ የሚያስፈልጉት ሁሉም ግብዓቶች ተሟልተው ያሉት ፀሐፊ ነው"
የአዳም ረታ አዲሱ 'መዝሙረ ሄላም' የተሰኘው የረዥም ልብ ወለድ መጽሐፍ 1,008 ገጾች ሲኖሩት በአምስት ክፍሎች የተከፈለ ነው። ይህ የአዳም አዲስ መጽሐፍ ከዚህ ቀደም የሚጠቀማቸው እንደ ሕፅናዊነት ያሉ ሥነ ጽሑፋዊ ቴክኒኮችን የያዘ መሆኑን በመጽሐፉ አርትኦት ላይ የተሳተፈው ቢኒያም አቡራ ለቢቢሲ ተናግሯል። የመጽሐፉ መቼት ከዚህ ቀደም እንደነበሩ የደራሲው ሥራዎች ከ1950ዎቹ ማለቂያ እስከ 70ዎቹ መጨረሻ ያሉ ናቸው። መጽሐፉ መጠሪያ የሆነችው ሄላም ከዋና ገጸባሕሪያቱ አንዷ ስትሆን በሁሉም ክፍል ውስጥ ትገኛለች። ለሕፅናዊነት አጻጻፉ ኹነኛ ማስተሳሰሪያ በመሆን ታገለግላለች። ቢቢሲ ከአርታኢው ቢኒያም ጋር ያደረገውን ቆይታ እነሆ. . .
አጃኢብ!
በኢትዮጵያ 55 በመቶ ሴቶች ሚስትን ለመደብደብ የሚያበቃ ምክንያት አለ ብለው እንደሚያስቡ ጥናት አሳየ
በኢትዮጵያ ከግማሽ በላይ የሚሆኑ ሴቶች ባል ሚስቱን ለመደብደብ አሳማኝ ምክንያት ይኖረዋል ብለው እንደሚያምኑ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት ያደረገው ጥናት አመለከተ። ሚስትን ለመምታት አሳማኝ ምክንያት እንዳለ የሚያስቡ ወንዶች ብዛት ከሴቶች ያነሰ ቢሆንም፤ ከዚህ ቀደም ከነበረው አንጻር በ11 በመቶ ጨምሮ ተገኝቷል።
የተመለሱ ጥያቄዎች
በአፍንጫ በሚገባ ውሃ አማካኝነት የሚከሰተው አንጎልን የሚያጠቃው አስፈሪው ተህዋስ
ባለፈው ዓመት በሕንድ በዚህ አንጎልን በሚያጠቃ ጥገኛ ተህዋስ የተያዙ ከ200 በላይ ሰዎች ተመዝገበዋል። ይህ ቁጥር በዓለም በአንድ አገር የተመዘገበው ከፍተኛው ሲሆን ከቅርብ ወራት ወዲህ በአገሪቱ እንዲህ ዓይነት ኬዞች መታየታቸውን ቀጥለዋል። ከዚህ በፊት በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገቡ የበሽታው ክስተቶች ከ500 ያነሱ ነበሩ።
ያለባቸው የጤና ችግር ሕክምና እንዲያጠኑ ያደረጋቸው ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
በረከት በቀለ፣ ኪምቢፊዳ በሚል ስም ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ይታወቃል። ወደ ቲክቶክ ብቅ ከማለቱ አስቀድሞ "በስፓይና ቢፊዳ (spina befida) የተያዝኩ ብቸኛው ሰው እኔ ብቻ እንደሆንኩ ይሰማኝ ነበር" ይላል። የአሊያንስ ፎር በርዝ ዲፌክት መሥራቹ ዶ/ር ነቢያት ተስፋዬም ልክ እንደ በረከት ሁሉ ከስፓይና ቢፊዳ (የነርቭ ዘንግ ክፍተት) ጋር ነው የተወለደው። አሁን 33 ዓመት እንደሆነው የሚናገረው ዶ/ር ነቢያት፣ በተወለደ በ22ኛው ቀን የስፓይና ቢፊዳ የቀዶ ሕክምና ተደርጎለታል። ሁለቱም ወጣቶች ከራሳቸው ህመም ተነስተው ሕክምና ለማጥናት መወሰናቸውን ለቢቢሲ ተናግረዋል።



































































































