ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ በእስራኤል ከ6 ሺህ በላይ ሰዎች ሆስፒታል ገብተዋል

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
ሁለተኛ ወሩን በጀመረው እስራኤል ከኢራን ጋር ከምታካሂደው ጦርነት ጋር በተያያዘ ከስድስት ሺህ በላይ ሰዎች ለሕክምና ወደ ሆስፒታሎች መወሰዳቸውን የአገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
እስካሁን ሆስፒታል ከገቡት መካከል 121 ሰዎች አሁንም ድረስ ሕክምና እየተደረገላቸው ነው። ከመካከላቸውም አንዱ በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን 16 ደግሞ ከባድ የሚባል ጉዳት የደረሰባቸው መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ደግሞ 232 ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በመላው አገሪቱ ወደ ሆስፒታሎች መሄዳቸውን የእስራኤል ጤና ሚኒስቴር ጨምሮ አሳውቋል።
እስራኤል ከአሜሪካ ጋር በማበር በኢራን ላይ ጥቃት መክፈቷን ተከትሎ ኢራን በእስራኤል ላይ የአጸፋ ጥቃቶችን እየፈጸመች ትገኛለች።
በሚሳዔሎች እና በድሮኖች የሚፈጸሙት ጥቃቶች በተለያዩ የእስራኤል አካባቢዎች ውስጥ የሚገኙ ቦታዎችን ዒላማ ያደረጉ ናቸው።














