ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ላይ ሊወሰዱ ስለሚችሉ ወታደራዊ አማራጮች ‘በሲቹዌሽን ሩም’ ሊሰበሰቡ መሆኑ ተዘገበ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ኢራን ላይ ሊፈጸሙ ስለሚችሉ ወታደራዊ አማራጮች ለመወያየት ማክሰኞ ዕለት ከፍተኛ የብሔራዊ ደኅነት አመራሮቻቸውን ይሰበስባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ አክሲዮስ ዘገበ።
የአሜሪካው የዜና ምንጭ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮችን ጠቅሶ ባወጣው ዘገባ፤ የፕሬዝዳንቱ የብሔራዊ ደኅንነት ቡድን አባላት ስለ ኢራን ለመወያየት ቅዳሜ ዕለትም ተሰብስበው ነበር።
ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫምስ፣ የዋይት ሃውስ መልዕክተኛ ስቲፍ ዊትኮፍ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ እና የሲአይኤ ዳይሬክተር ጆን ራትክሊፍ ከተሰብሳቢዎቹ መካከል ነበሩ ተብሏል።
ትራምፕ ለአክሲዮስ በሰጡት ቃለ መጠይቅ፤ ከኢራን ጋን ስምምነት ላይ ይደረሳል ብለው እንደሚያስቡ ተናግረዋል።
የኢራን የድርድር ዕቅድ ላይ የሚደረገውን ማሻሻያ እየጠበቁ መሆኑን የተናገሩት ፕሬዝዳንቱ፤ ከቀናት በፊት ከቀረበው የተሻለ ይሆናል ብለው ተስፋ እንደሚያደርጉም ጠቅሰዋል። ለድርድሩ ቀነ ገደብ ከማስቀመጥ ግን ተቆጥበዋል።
“ስምምነት መፈጸም እንፈልጋለን። እንዲሆኑ የምንፈልገው ቦታ ላይ አይደሉም። እዚያ መረድስ አለባቸው ወይም ክፉኛ ይመታሉ፤ ያንን ደግሞ አይፈልጉም” ብለዋል።
አሜሪካ እና ኢራን ከመጀመሪያው ዙር ድርድር በኋላ ንግግሩን ለማስቀጠል አልተገናኙም።
አሸማጋይ ሆና እየተንቀሳቀሰች ያለቸው ፓኪስታን ቅዳሜ ዕለት የአገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትሯን ወደ ቴህራን ልካ ነበር። ድርድሩን ለማስጀመር እሑድ ዕለትም ከኢራን ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ሲነጋገሩ ነበር።



